tg-me.com/Golden_Speech/9280
Last Update:
በጣም ይዋደዱ ነበር ! ነገርግን ሸይጧን ማሀላቸው ገብቶ አጋጫቸው ለመኮራረፍም ዳረጋቸው. በጧት ተነስታ ቁርሱን ሰርታ ገበታው ላይ አቅርባለት ትታው ወደ ሌላ ስራዋ ገባች. እሱም ከንቅልፉ ተነስቶ ቁርሱን ለመብላት ገበታው ላይ ታደመ ነገር ግን ከጎኑ ያቺ ሚወዳት ሚስቱ የለችም .ምግቡን ለመብላት ቢፈልግም ግን አልተቻለውም እሷ ነበረች እያጫወተች ምታጎርሰው በቃ የምግቡ ጣእምም አልመጣለት አለው ...
ወደ ማድ ቤቱ በመመልከት እንደ ከዚህ በፊቱ የሚስቱን መምጣት መጠባበቅ ጀመረ.ከማድ ቤት ዳቦ ይዛ አጠገቡ ልትቀመጥ ብትሞክርም አልቻለችም ትናንተ እንደዛ ሰድቧትና አስቀይማት ይቅርታ አለማለቱ አናዷታል.
ዳቦውን አስቀምጣለት ወደ ማድ ቤት በመመለስ እቃዎችን ማፀዳዳት ጀመረች በስራዋም ላይ ሳለች የበር ድምፅ ሰማችና ስትሄድ ባሏ ከቤት ወጥቶ ሂዷል .የበላበትን ለማነሳሳት ስትሄድ ያዘጋጀችው ምግብ አንድም ሳይነካ እንዳለ ነው ...
አዎ ያለኔኮ አይበላህም እኔ እነዳጎርስህና እንዳጠጣህ ፈልገህ ነበር ,ይህ ደሞ ላንተ አይገባህም አንተ እኔ እነደምከባከብህ ሞራሌን መጠበቅ አትችልበትም እያለች ከራሷጋ አወራች .. ምግብ ሳይበላ መሄዱ ግን አሳዝኗታል...
በሀሳብ ተውጣና አዝና ሱፍራውን ለማንሳት ስትል ሁለት አበባ ተመለከትች አንዱ ነጭ እና አንድኛው ቀይ ናቸው አበባዎቹ ከስራቸው ወረቀት ተቀምጧል ለካስ ደብዳቤ ፅፎ ኖሯል...
በአላህ ስም እጅግ በጣም አዛኝ በጣም ሩህሩህ በሆነው ይላል መግቢያው «ይድረስ በሂወቴ ፍፁም ውብ ለሆነችዋ አበባዬ፣ ለውዷ ሚስቴ፣ ሂወቴና እንከወዳኘው የምወዳት ለሆነችዋ...የአላህ ሰላምና እዝነት ባንቺ ላይ ይሰፈን.
የኔ ፍቅር
ዛሬ አብረሽኝ ቁረስ እንድትበዪ ምንኛ ጓጉቼ ነበር ነገርግን አለመምጣትሽን ሳይ ያለልማዴ አንቺን ከጊኔ አጥቼ አንድም ጉርሻ ሊወርድልኝ አልቻለም.
ዛሬ ያ በር ላይ ሁነሽ የምትሰቺኝ ፈግግታሽን መመልከት ምንኛ አጓግቶኝ ነበር ነገር ግን ያ ሳይሆን ቀርቶ ከፍቶኝና ቀልቤ ተሰብሮ ወጣው ...
የኔ ፍቅር
ሸይጧን አሸንፎኝ ሀቅሽን በማጉደል አጠፍቻለው ይቅርታዬን ትቀበዪኝ ይሆን ⁉»ይላል ..
🥺🥺🥺🥺
አይኖቿ በእንባ ተሞሉ ወረቀቱን እቅፍ አርጋ እያለቀሰች ሳመችው :አንተም ይቅርታ አርግልኝ የኔ ውድ ባል አለች..
ከዛ እንደ ንብ ተነስታ ቤቷን ማዘገጃጀት ጀመረች ቤቷን ሌላ አለም አደረገችው ያ የትናንቱ ቤት አይመስልም አቤት ውበት !
ለባሏም ሚወደውን ምሳ አዘጋጀች መምጫው ሰአት ሲደርስ የመዋብን ጥግ ተውባ ደስስ በሚል ፈገግታ ከበሩ ቁማ ተቀበለችው እሱም ሁኔታው አስደስቶት ለጥፋቱ ድጋሚ ይቅርታን ጠየቀ ዳግም እንደማይመለስበትም ቃል ገባ!
ባሎች ይቅርታ መጠየቅ ይልመድባችሁ !
ሚስቶች ደሞ ሳትግደረደሩ ይቅርታን ተቀበሉ!
ላጤዎች ደሞ አግቡ ዝምብላቹ የሰው ታሪክ አታንብቡ ‼
አግቡና የናንተንም ታሪክ እንፃፍላችሁ‼
BY ወርቃማ ንግግሮች
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280
Share with your friend now:
tg-me.com/Golden_Speech/9280